የቆላ ቀርከሃን ለማባዘት የሚያስችል ፕሮቶኮል ለማውጣት የተደረገው ምርምር ውጤታማ ሆኗል

EFRI, 04/11/2020

ኢንስቲትዩታችን (የኢትዮጵያ የአካባቢና የደን ምርምር ኢንስቲትዩት)ከአማራ መልሶ ማቋቋም ልማት ድርጅት (አመልድ) እጽዋት ቲሹ ካልቸር ላብራቶሪ ጋር በመተባበር ላለፉት ሁለት አመታት የቆላ ቀርከሃን በብዛት ለማባዘት የሚያስችል ፕሮቶኮል ለማውጣት የተደረገው ምርምር ውጤታማ ሆኗል፡፡

በአሁኑ ጊዜ ፕሮቶኮሉን በመጠቀምና ችግኝ በማምረት በተለያየ ሰው ሰራሽ ችግር ምክንያት በተራቆተው የአባይ ተፋሰስ የሚገኘውን የተወሰነውን ቦታ በቆላ ቀርከሃ ለመሽፈን እጽዋቱ በብዛት እየተባዛ ይገኛል ፡፡

ማስታዎሻ፤ የቆላ ቀርከሃ ቶሎ የማደግ ባህሪ እና ለኢኮኖሚያውና ለአካባቢ ጥበቃ ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው እፅዋት ነው። ይሁን እንጅ ቀርከሃ ለማበብና ዘር ለማፍራት ከ20 – 120 ዓመታት ያላነሰ ጊዜ ይፈልጋል። ሌላው ችግር ከአበበና ከአፈራ በኋላ በአንድ ጊዜ የመሞት እድሉ ከፍተኛ መሆኑ ነው። ይህ የምርምር ውጤት ችግሩን በእጅጉ እንደሚቀርፍ ይታመናል።

EEFRI in collaboration with ORDA tissue culture laboratory has developed a protocol for mass production of Lowland bamboo seedlings. The seedlings will be planted in the Abay River basin, which is degraded by anthropogenic factors.

Note: Lowland bamboo is fast growing, and has immense benefits for the economy and Environmental conservation and rehabilitation. The bamboo takes from 20-120 years to flower and fruit and dies in mass. This research output helps to tackle such challenges significantly.

Related posts