በቀርካሃ ላይ ሲሰራ የነበረው የላብራቶሪ የምርምር ስራ የተራቆቱ ቦታዎችን ቶሎ እንዲያገግሙ ማድረግ የሚያስችል ነው

EEFRI, 04/11/2020, Addis Ababa የኢትዮጵያ የአካባቢና የደን ምርምር ኢንስቲትዩት ከአማራ መልሶ ማቋቋም ልማት ድርጅት (አመልድ) እጽዋት ቲሹ ካልቸር ላብራቶሪ ጋር በመተባበር ላለፉት ሁለት አመታት የቆላ ቀርከሃን በብዛት ለማባዘት የሚያስችል ፕሮቶኮል ለማውጣት የተደረገው ምርምር ውጤታማ ሆኗል፡፡ በዓለማችን ከ1600 በላይ የቀርከሃ ዝርያዎች ሲኖሩ በኢትዮጵያ ሀገር በቀል የሆኑ የቆላና የደጋ የሚባሉ ሁለት የቀርከሃ ዝርያዎች እንዳሉ መረጃዎች ያሰረዳሉ፡፡ ቀርከሃ በዘሩ መራባት የሚችል ቢሆንም ፍሬውን ለማግኘት በረጅም አመት አንድጊዜ የሚያብብ በመሆኑና በተለያዩ ተባዮችና በሽታዎች ምክንያት በአንድ ጊዜ ብዙ ዘር ለማግኘት አስቸጋሪ ነው፡፡

Read More

የቆላ ቀርከሃን ለማባዘት የሚያስችል ፕሮቶኮል ለማውጣት የተደረገው ምርምር ውጤታማ ሆኗል

EFRI, 04/11/2020 ኢንስቲትዩታችን (የኢትዮጵያ የአካባቢና የደን ምርምር ኢንስቲትዩት)ከአማራ መልሶ ማቋቋም ልማት ድርጅት (አመልድ) እጽዋት ቲሹ ካልቸር ላብራቶሪ ጋር በመተባበር ላለፉት ሁለት አመታት የቆላ ቀርከሃን በብዛት ለማባዘት የሚያስችል ፕሮቶኮል ለማውጣት የተደረገው ምርምር ውጤታማ ሆኗል፡፡ በአሁኑ ጊዜ ፕሮቶኮሉን በመጠቀምና ችግኝ በማምረት በተለያየ ሰው ሰራሽ ችግር ምክንያት በተራቆተው የአባይ ተፋሰስ የሚገኘውን የተወሰነውን ቦታ በቆላ ቀርከሃ ለመሽፈን እጽዋቱ በብዛት እየተባዛ ይገኛል ፡፡

Read More