የደን ቃጠሎን በጋራ እንከላከል

(ወቅታዊ መልዕክት) 12 ጥር 2012: ደን በተለያዩ ነገሮች ተፅዕኖ ሊደርስበት ይችላል፡፡ በአለም ዙሪያ ከፍተኛ ችግር ከሚያደርሱ ምክንያቶች አንዱና ዋነኛው ደግሞ የሰደድ እሳት ነው፡፡ በአለም ደረጃ በየዓመቱ በሰደድ እሳት በብዙ ሺህ ሄክታር የሚደርስ ደን የሚወድም ሲሆን በኢትዮጵያም እሰከ መቶ ሺህ ሄክታር ደን ላይ ጉዳት እንደሚደርስ መረጃዎች ያሳያሉ፡፡ የቃጠሎው መንስዔ የተለያየ ቢሆንም በኢትዮጵያ በአብዛኛው ሰው ሰራሽ ችግር ነው፡፡ ሰዎች የእርሻ ማሳቸውን ለማዘጋጀት በሚያደርጉት የማቃጠል ሂደት እና በጫካ ማር ቆረጣ ሂደት በሚደረጉ እንቅስቃሴዎች እንደሆኑ የተደረጉ የዳሰሳ ጥናቶች ይጠቁማሉ፡፡ በኢትዮጵያ ከጥር እስከ መጋቢት ባሉት ነፋሻማና ሞቃት የአየር ሁኔታ በሚጠናከርበት ወቅት የደን ቃጠሎ በብዛት ይከሰታል፡፡ …

Read More

የደን ሀብት ዘላቂ ልማት ትኩረት ይሻል

ዛፍን በመትከል አለማችንን የተሻለች በማድረግ ከፍተኛ ተፅዕኖ ማምጣት ይቻላል፡፡ ዛፍን በአግባቡ ከያዝነው ቁሳቁስና የተለያዩ ግልጋሎቶችን በመስጠት ከፍተኛ ጠቀሜታ ይሰጠናል፡፡ ዛፍ ከጠፋ ቀጣይነት ያለው ህይወት ጥያቄ ውስጥ ይገባል፡፡ የዛፎች መኖር የህልውና ዋስተና ናቸው፡፡ ደን ሊሻሻል፣ ሊያድግ እና ሊጠበቅ የሚችል ታዳሽ የሆነ ሃብታችን ነው፡፡ ዓለምን የተሻለች ለማድረግና ለማስቀጠል ዛፍን እንደመትከልና መንከባከብ የመሰለ አስደሳችና ቀላል ዘዴ የለም፡፡ በ1992 በተደረገው የመሬት ጉባኤ (Earth Summit) ብዝሀ ሕይወት፤ የአየር ንብረት ለውጥና በረሃማነት ጉዳይ ጀምሮ ስለደን በተደጋጋሚ ትኩረት እንዲሰጠው የተወሰነ ሲሆን በተለይ በ2012 በተደረገው የሪዮ ስብሰባ የዓለም መንግስታት የተቀናጀ የዘላቂ ልማት በኢኮኖሚ በማህበራዊ እና በአካባቢያዊ ዘርፎች እንዲረጋገጥ…

Read More